Holy Pictures of EOTCቅዱሳን ስዕላት ikon

4.5.1 by Samuel Minale


Feb 28, 2024

Mengenai Holy Pictures of EOTCቅዱሳን ስዕላት

Malaysia

Senarai Ethiopian Orthodox Tewahedo Gereja Holy Gambar & MontlyYearly Hari-hari Raya

APLIKASI ini mengandungi lebih daripada 400 Gambar Suci yang berbeza dari Orang Suci Gereja Tewahedo Ortodoks Ethiopia, Malaikat Suci, Bapa Suci, Ibu Suci, dan Gambar Suci Tuhan dengan Senarai Hari Suci Tahunan, Bulanan yang disambut di Gereja Ortodoks Tewahedo dan akhirnya aplikasi mengandungi senarai nama alkitabiah dan sebutan mereka.

Harap perhatikan bahawa gambar-gambar Suci yang terdapat dalam aplikasi ini bukan satu-satunya gambar terdapat banyak Orang Suci yang tidak termasuk dalam Aplikasi ini.

በዚህ መተግበሪያ ውስጥ ከ 400 በላይ የቅዱሳን ስዕላትን በማንኛውም ጊዜ ማግኘት እንዲችሉ ካለ ኢንተርኔት እንዲሰራ በመተግበሪያው ውስጥ ስእላቱ እንዲካተቱ ተደርጎዋል ፡፡

ከቅዱሳኑ በረከት ረድኤት ይደርብን

አሜን !!!

ከዚህ በታች ያለው አቡነ ገብርኤል በ 1990 ካሳተሙት “ክብረ ቅዱሳን» ከሚለው መጻሕፍ የተወሰደ ነው

የጥንቱና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚከተል ክርስቲያን ሁሉ ከቅዱሳት ሥዕሎች ሁለት ዐበይት ጥቅሞችን ያገኛል ይኽውም ትምህርትና ረድኤት ናቸው። ይልቁንም ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረው ቃለ እግዚአብሔር (አካላዊ ቃል) በኋለኛው ዘመን ሰውን ለማዳን ወደዚህ ዓለም መጥቶ ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ተፀንሶ ከሥጋዋ ሥጋን ፣ ከነፍስዋ ነፍስን ነስቶ ከኃጢአት ብቻ በቀር ፍጹም ሰው ሆኖ የተወለደውና ተሰቅሎ ተሰቅሎ በሞቱ ዓለሙን ማዳኑን በሥዕል ገልጾ ማቅረብ መስበክ መስበክ ፤ ማስተማር ነው። በዚህም መሠረት የጌታችንን የልደቱን ታሪክ ፣ የጥምቀቱን ታሪክ ፣ የስቅለቱን ታሪክ ፣ የትንሣኤውንና የዕርገቱን ታሪክ በሥዕል ነድፎ ለምእመናን ማቅረብ ማለት የጌታችንን ወንጌለ መንግሥት መስበክና ማስተማር ማለት ነው ምክንያቱም ሥዕል ራሱበጉልህ የተጻፈ ጽሑፍ ማለት ነውና። ጌታችን ተወለደ ፣ ተጠመቀ ፣ ተሰቀለ ፣ ሞተ ፣ ከሙታን ተለይቶተነሣ… የሚለው የወንጌሉ ታሪክ በሥዕል ማቅረብ ማለት ታሪኩን በጉልህ ጽፎ ማቅረብ ማለት ነው።

ሲጽፍ ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ክርስቲያኖች ተግሳጽ የማታስተውሉ «የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ ፤ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ እንደተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር »ያለው ኢየሱስና ታሪኩን በሚገባ አውቀውትና ከልብም ተረድተውት እንደ ነበር ለመግለጽ ነው (ገላ .3 ፤ 1-2)

ስለዚህ ከላይ እንደተገለጸው ቅዱሳት ሥዕሎች በመመልከትና ልብ ብሎ በማንበብ (በማስተዋል) ታሪኩን በሚገባ ማወቅና መረዳት ስለሚቻል ፤ ስለዚህ በቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ሥዕሎች የክርስትና ሃይማኖት አስተማሪዎችና አስረጂዎች መሆናቸውን መገንዘብ ተገቢ ነው።

ሁለተኛው ጥቅም ከቅዱሳት ሥዕሎች የሚገኘው ሌላው ዐቢይ ጥቅም ደግሞ ረድኤት (ርዳታ) ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ በነበረበት በጣም ቅርብ የነበሩት የጥንት ክርስቲያኖች በጌታችን ሥዕል ፣ በቅድስት ድንግል ሥዕልና በቅዱሳን ሥዕሎች ይማፀኑ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይመሰክራል። በዘመናችን ተቆፍረው የተገኙ የጥንት አብያተ ክርስቲያናት ፍርስራሶችም በሥዕላተ ቅዱሳን መማፀን ጥንታዊ ትውፊት (ሥርዓት) እንደሆነ ያመለክታሉ ታሪክን መካድ ደግሞ አያትና ቅድመ አያትን መካድ ማለት ነው። ስለ ሥዕል ክብር የቤተ ክርስቲያን ትውፊታዊ ታሪክ ምስክር ነው። የታወቀው ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊ አውሳብዮስ ኤጲስ ቆጶስዘቂሳርያ ስለ ጌታ ሥዕል አጀማመርና አመጣጥ ጽፎ ያቀረበውን ብፁእ አባ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳስ ዘሸዋበመጽሐፋቸው ጠቅሰውታል። አኛም የጥቅሱን ፍሬ ነገር ቀጥለን ጠቅሰነዋል።

«ንጉሥ ዐብጋር በዑር (ኤዴሣ ከተማ የአገሩ ንጉሥ በመሆን ጌታችን በነበረበት ዘመን ይኖር ነበረ ፤ ስሙም (ልዑካን) ይባል ነበር። ዐብጋር ማለት በከለዳውያን ቋንቋ ቄሣር ማለት ነው። ዐብጋር በዚያ ዘመን በጠና ነበር ፤ የጌታችንን ተአምራት በዝና ሰምቶ ይፈውሰው ዘንድ ደብዳቤ ጽፎ ለጌታችን ለጌታችን ላከለት ፤ ጌታችንም ደብዳቤውን ከመልእክተኛው እጅ ካነበበው በኋላ «ሳያየኝ ያመነኝ ዐብጋር ብፁዕ ነው» ብሎ ዐብጋርን በማመስገን በሱ ስም እንዲፈውሰው ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱን እንደሚልከለት በመግለጽ መልስ ላከለት። ነገር ግን ከጌታ ጋር ተገናኝቶ የተመለሰው የዐብጋር (ዩካማ) መልእክተኛ ሠዓሊ ስለነበር ከጌታችን ጋር ሲነጋገር ፊቱን በሥዕል ነድፎ (ሥሎ) ከደብዳቤው ጋር ይዞ ተመለሰ። ከዚያም አንደ ደረሰ ከጌታ የተላከውን ደብዳቤ ለታመመው በዚያን አነበበለት ፤ ሥዕሉንም አሳየው። በዚያን ጊዜ በሽተኛው ንጉሥ የጌታችንን ቃል ከደብዳቤው ሰምቶና ሥዕሉንም በዓይኑ ተመልክቶ ወዲያው ከሕመሙ እንደ ተፈወሰ ታሪኩ ያስረዳል (አባ ጎርጎርዮስ ፤ የኢ ኦ ተ ቤተ ክርስቲያንታሪክ 1974 ገጽ 119 120)።

ይኽው አውሳብዮስ ስለ ጌታችን የሰጠው ምስክርነት ምስክርነት እንዲህ የሚል ጌታችን ኢየሱስ ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ደሙን እያንጠፈጠፈ መስቀሉን ተሸክሞ ወደ ጎልጎታ በሚጓዝበት ወቅት እያለቀሱ ከሚከተሉት ደጋግ ሴቶች መካከል ቬሮኒካ የተባለች ደግ ሴት የራስዋን መሸፈኛ አውልቃፊቱን አንዲያድፍበት (እንዲጠርግበት ስጌታ ወረወረችለት ፤ ጌታችንም በደምና በላብ የተጠመቀውን የተጠመቀውን ሥዕለ ሲመልስላት ሲመልስላት ሲመልስላት ሲመልስላት ሲመልስላት ገጹ ማለት የፊቱ መልክ በሻሽዋ ላይ ታትሞ ቀረ »በማለት ከላይ የጠቀስነው የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስ ይመሰክራል።

ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ደግሞ ወላዲተ አምላክ በነበረችበት ክፍለ ዘመን የነበረው ሐዋርያው ​​ቅዱስ ያዕቆብ የጌታን ታሪክ (ወንጌል) ሲጽፍ ስለ ወላዲተ አምላክም ብዙ ጽፎአል። በዚህ የያዕቆብ ወንጌል (ያዕቆብ ታሪክ) በተባለው የትውፊት መጽሐፍ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ለመጀመሪያ ጊዜ የማርያምን ሥዕል መሃሉ ተጽፎአል።

አውሳብዮስ ኤጲስ ቆጶስ ዘቂሳርያና ሌሎችም የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች እንደ መሰከሩት የጥንትዋ ቤተ ክርስቲያን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥዕል ፣ ለወላዲተ አምላክ ፣ ለቅዱሳን መላእክት ፣ ለጻድቃንና ለሰማዕታት ሥዕሎች ከፍ ያለ ክብር እንዲደረግላቸውና የጸጋና የአክብሮት ስግደት እንዲቀርብላቸው ስታስተምር ኖራለች።። ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት በሚጸልዩበት ቤተ ክርስቲያንና በቤታቸው በሚገኘው በግል ጸሎት ቤታችው የጌታችንን ፣ የቅድስት ድንግል ማርያምና ​​የቅዱሳንን ሥዕሎች በግድግዳው በመስቀልና የክብር ስግደት በማቅረብሲማፀኑባቸው ኖረዋል።።

በዚሁ ሁኔታ የሥዕል ክብር በጥንትዋ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተጠበቀ አስከ ስምንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ ከቆየ በኋላ ሳይታሰብ በድንገት ከክርስቲያኖቹ መካከል ጥቂቶች ሰዎች የሥዕልን ክብር በመቃወም ተነሡ። በዚሁ ምክንያት በሮምና በቢዛንታይን ግዛቶች ከባድ ክርክርና ሁከት ተቀሰቀሰ። በ ጊዜ በ 797 ዓም የምስራቅቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጉባዔ አድርገው የቅዱሳንን ሥዕሎችማክበርና መሳም (መሳለም) እንደሚገባ ለሥዕሎቹም የአክብሮት ስግደት ማቅረብ ተገቢ መሆኑን በሰፊው አትተው ወስነዋል ... ቀሪውን ከዌብሳይቱ ላይ ያንብብቡ

Apa yang baru dalam versi terkini 4.5.1

Last updated on Feb 28, 2024

Sharing Holy Picture is now added
More Holy Pictures Added
Some bugs fixed specially for android 5+ users
bugfix

Terjemahan Memuatkan...

Maklumat APLIKASI tambahan

Versi Terbaru

Minta Holy Pictures of EOTCቅዱሳን ስዕላት Kemas kini 4.5.1

Dimuat naik oleh

اطياف راحلة

Memerlukan Android

Android 5.0+

Available on

Dapatkan Holy Pictures of EOTCቅዱሳን ስዕላት melalui Google Play

Tunjukkan Lagi

Holy Pictures of EOTCቅዱሳን ስዕላት Tangkapan skrin

Memuatkan Komen...
Bahasa
Mencari...
Langgan APKPure
Jadilah yang pertama untuk mendapatkan akses kepada pelepasan awal, berita, dan panduan permainan dan aplikasi Android terbaik.
Tidak, Terima kasih
Daftar
Berjaya berjaya!
Anda kini melanggan APKPure.
Langgan APKPure
Jadilah yang pertama untuk mendapatkan akses kepada pelepasan awal, berita, dan panduan permainan dan aplikasi Android terbaik.
Tidak, Terima kasih
Daftar
Kejayaan!
Anda kini melanggan surat berita kami.